No worries! You can check out similar opportunities — Just Click Below.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከዚህ በታች በተጠቀሰው ክፍት የስራ መደብ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል። የስራ መደቡ መጠሪያ፡ ኤክስኪዩቲቭ ሴክሬታሪ I የስራ ደረጃ፡ IX ደመወዝ፡ 4,150 ብዛት፡ 2 የትምህርት ዓይነትና ተፈላጊ የስራ ልምድ፡ በጽህፈትና የቢሮ አስተዳደር /በሴክሬታሪያል ሳይንስና ኦፊስ ማኔጅመንት/ ዲፕሎማ ወይም የቴክኒክ ሙያ በደረጃ 3 የማረጋገጫ ብቃት ማስረጃ /10+3/ እና 4 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት ማሳሰቢያ፡ የምዝገባ ቀን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ተመዝጋቢዎች የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። አመልካቾች የስራ ልምድ ለሚጠይቁ ክፍት የስራ መደቦች ላይ አግባብነት ያለው የስራ ልምድ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። በሌቭል የትምህርት ዝግጅት ለጨረሱ አመልካቾች የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት /COC/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ከዝቅተኛ ተፈላጊ በላይ የሚጠይቁ የትምህርት ዝግጅቶች ለውድድር መቅረብ አይችሉም። የምዝገባ ቦታ ሜክሲኮ ሰንጋ ተር 40/60 ኮንዶሚንየም ፊት ለፊት ዮቤክ ሕንጻ 8ኛ ፎቅ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የሰው ኃይል አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡ 011 557 91 99