Position Title: ባለክሬን የጭነት መኪና ኦፕሬተር ረዳት
Employer: Abyssinia Bank
Employment: Full-Time | Permanent
Place of Work: Addis Ababa - Ethiopia
Posted date: 2 hours ago
Deadline: February, 27/2026 (4 days left)
የሥራ ዓላማ
የባንኩን ንብረት በተገቢው ሰዓት በሚፈለግበት ቦታ ላይ በጥንቃቄ ለማድረስ የተጫኑ ዕቃዎች በጉዞ ወቅት እዳይጎዱ በተገቢው ሁኔታ ማሰር፣ ሸራ ማልበስ፣ መድረሻ ቦታ ላይም በጥንቃቄ ማድረግ፤ ከኦፕሬተሩ በሚሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መፈፀም ይሆናል፡፡
ባለክሬን የጭነት መኪና ኦፕሬተር ረዳት / Assistant to the Crane Mounted Truck Operator / ዝርዝር ተግባራት:
- ሥራ ከመጀመሩ በፊት የሞተር ዘይት፣ ውሃ፣ መብራት፣ የጎማ ነፋስና የመሳሰሉትን ነገሮች መሟላታቸውን ማረጋገጥ።
- የባንኩን ከባድ ወይም መካከለኛ የጭነት መኪና ከያዘው ኦፕሬተር/ሹፌር ጋር በመሆን በከተማም ሆነ ከከተማ ውጭ ዕቃ በማጓጓዝ አገልግሎት ለሚሰጠው ኦፕሬተር ልዩ ልዩ ድጋፍ ማድረግ፡፡
- ለተሽከርካሪው የሚያስፈልጉ ነገሮች እንደ ነዳጅ፣ መጠባበቂያ ጎማና የመፍቻ ዕቃዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ።
- ጉዞ ከጨረሰ በኋላ የተሽከርካሪው የተሸከርካሪው ጎማ፣. አረግራጊ ክፍሎች እና ፍሳሽ ሊኖራቸው የሚችሉ ቦታዎችን ደህንነት ያረጋግጣል፡፡ ችግር ካለ ለኦፕሬተሩ ወዲያውኑ ማሳወቅ፡፡
- በማሽን ተነስተው የሚጓጓዙ የኤ.ቲ.ኤም ማሽንና ሌሎችንም ዕቃዎች በጥንቃቄ ያነሳል በተገቢው ቦታ ማውረድ፡፡
- እንዲያደርስ የተረከበውን ንብረት /የኤቲኤም ማሽን፣ካዝና.../ ቆጥሮ ለሚመለከተው አካል በማስረከቡ ረገድ ኦፕሬተሩን መርዳት፡፡
- የተሽከርካሪውን ደህንነት በሚገባ መጠበቅ።
- ተሽከርካሪው በብልሽት ምክንያት ለጥገና ጋራዥ ሲገባ ክትትል ማድረግ ፤ በትክክል መሠራቱንም ማረጋገጥ፤ ሁኔታውን ለኦፕሬተሩ ማሳወቅ፡፡
- ቦሎና ሌሎች እንዲለጠፉ የተጠየቁ ሰነዶች በተፈቀዱ የሽከርካሪው አካል ላይ መለጠፍ።
- በስራ ሰዓት የባንኩን የደንብ ልብስ ንጽህናውን ጠብቆ ማልበስ።
- ከቅርብ የስራ ሀላፊው የሚሰጡ ሌሎች ተያያዥ ስራዎችን ማከናወን።
የትምህርት ደረጃ ትምህርት፡-
- 10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ። የሶስተኛ ደረጃ ወይም የጭነት መኪና I የመንጃ ፈቃድ፤ እና በቴክኒክ ትምህርት የምስክር ወረቀት ያለዉ።
- የስራ ልምድ፡--ቢያንስ 2 ዓመት ተዛማጅ የስራ ልምድ። በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ልም ያለዉ።