Position Title: Now Recruiting: Driver
Employer: Abyssinia Bank
Employment: Full-Time | Permanent
Place of Work: Addis Ababa - Ethiopia
Posted date: 2 hours ago
Deadline: March, 07/2026 (4 days left)
የሥራ ዓላማ: ለስራ ወደ ተለያዩ ስፍራዎች የሚንቀሳቀሱ የባንኩን ሰራተኞች ወይም ዕቃ/ንብረት ከቦታ ቦታ ማጓጓዝና በኃላፊነት የተሰጠውን ተሽከርካሪ በአግባቡ እና በጥንያቄ በመያዝ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ይሆናል፡፡
ሾፌር /Driver I / ዝርዝር ተግባራት:
- ሥራ ከመጀመሩ በፊት የሞተር ዘይት፣ ውሃ፣ መብራት፣ የጎማ ነፋስና የመሳሰሉትን ነገሮች መሟላታቸውን ማረጋገጥ።
- የባንኩን ከባድ፤ መካከለኛ፤ አነስተኛና ቀላል ተሽከርካሪዎች በመያዝ በከተማም ሆነ ከከተማ ውጭሠራተኞች ወይም ዕቃ በማጓጓዝ አገልግሎት መስጠት።
- ለተሽከርካሪው የሚያስፈልጉ ነገሮች እንደ ነዳጅ፣ መጠባበቂያ ጎማና የመፍቻ ዕቃዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ።
- በመስክ ሥራላይ ለተሽከርካሪው የሚያስፈልጉ ነገሮች እንደ ነዳጅና ሌሎች ዕቃዎችን ሲያስፈልጉ በህጋዊ ደረሰኝ መግዛት፤ እንዲሁም ማወራረድ።
- ጉዞ ከመጀመሩ በፊትና ከጨረሰ በኋላ የተሽከርካሪው የኪሎ ሜትር ቆጣሪ መነሻና መድረሻ ቁጥሮችንና የሄደባቸው ቦታዎችን በተዘጋጀው ቅጽወይም ፎርም ላይ መመዝገብ።
- ለተሽከርካሪው የሚያስፈልጉትን መለዋወጫና እድሳት በመከታተል ለክፍል ኃላፊው ወይም ለትራንስፖርት አስተዳደር በወቅቱ ማሳወቅ።
- አነስተኛ ጥገናዎችን ያከናውናል፤ ከአቅም በላይ የሆነ ብልሽት ሲያጋጥም ሁኔታውን ወዲያው ለትራንስፖርት አስተዳደር ማሳወቅ።
- እንዲያደርስ የተረከበውን ንብረት በአግባቡ ቆጥሮ ለሚመለከተው አካል ማስረከብ።
- የተረከበውን ተሽከርካሪ ደህንነት በሚገባ መጠበቅ።
- ተሽከርካሪው በብልሽት ምክንያት ለጥገና ጋራዥ ሲገባ ክትትል ማድረግ ፤ በትክክል መሠራቱንም ማረጋገጥ፤ እንደአስፈላጊነቱም ሁኔታውን ለክፍል ኃላፊው ወይም ለሚመለከተው አካል በወቅቱ ማሳወቅ።
- ተሽከርካሪው በወቅቱ ሰርቪስ እንዲደረግለት መጠየቅ።
- ተሽከርካሪውን በየዓመቱ ማስመርመር።
- ቦሎና ሌሎች እንዲለጠፉ የተጠየቁ ሰነዶች በተፈቀዱ የሽከርካሪው አካል ላይ መለጠፍ።
- በስራ ሰዓት የባንኩን የደንብ ልብስ ንጽህናውን ጠብቆ መልበስ::
- ከቅርብ የስራ ሀላፊው የሚሰጡ ሌሎች ተያያዥ ስራዎችን ማከናወን።
መስፈርቶች
- የትምህርት ደረጃ፡- 12ኛ/10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ፤ እና የመንግስት የመጀመሪያ ወይም የሶስተኛ ደረጃ የመንጃ ፈቃድ ያለው።
- የስራ ልምድ፡- ቢያንስ 2 አመት የመንዳት ልምድ ያለው። በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ የስራ ልምድ ጠቃሚ ነው።